Association for Human Rights in Ethiopia

  • About
  • Key Resources
  • Publications
  • Archives
  • Contact Us
  • Ethiopia: Killings, arrests under new State of Emergency
  • Ethiopia arrests 30 journalist, bloggers and activists
  • Joint civil society letter to Ethiopian Prime Minister-designate on recent arrests of journalists and human rights defenders
  • Joint civil society letter to Ethiopian Prime Minister-designate on recent arrests of journalists and human rights defenders
  • Facebook

Powered by Genesis

የነሐሴ ወር 2012 የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በኢትዮጵያ

10th September 2020 by Admin

ጋዜጣዊ መግለጫ

ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ በነሐሴ ወር በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብት አያያዝ ረገድ የተስተዋሉ ዋና ዋና ክስተቶችን መሰረት በማድረግ ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶል፡፡ ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ 

በደቡብ ብ/ብ/ህ/ ክልላዊ መንግስት የወላይታ ዞን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በነበረው ግጭት የንፁኃን ህይወት ማለፉን በመንግስት አካላት፤ እንዲሁም በተለያዩ የመብት ተሟጋች ቡድኖች ተገልፆል፡፡ አንዳንዶችም የፀጥታ ኃይሉ ያልተመጣጠነ የኃይል እርምጃ በመውሰዱ ምክንያት ለብዙዎች ሞት እና ለብዙዎች አካል መጉደል መንስኤ ሊሆን እንደቻለ ዘግበዋል፡፡  

በሌላ በኩል በኦሮሚያ ክልል ለተቃውሞ በተጠሩ ሰልፎች ለመሳተፍ ወደ አደባባይ በወጡ ግለሰቦች እና በፀጥታ ሀይሎች መካከል በተከሰተው ግጭት ምክንያት የሰዎች ህይወት መጥፋቱ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎ ነሐሴ 14 ቀን 2012 ዓ.ም  የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ የፀጥታ ሀይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል ከመጠቀም እንዲቆጠቡ ጥሪውን አቅርቦል፡፡ 

የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በተከሰተው የሰላም መደፍረስ እና የሰብአዊ መብት ጥሰት ለማጥናት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ያደረገው ጥረት የሚያበረታታ ቢሆንም እሰከአሁን ድረስ ሙሉ ሪፖርት ግን አልቀረበም፡፡ ነሐሴ 8 ቀን /2012 ዓ/ም የወጣው የሰብአዊ መብት ኮሚሽኑ መግለጫ እንደሚያመለክተው አሁንም ቢሆን ጥቃቱ በተፈጸመባቸው አንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች የጥቃቱ ኢላማ የሆኑ ዜጎች አሁንም የጥቃት ስጋት ያለባቸው መሆኑን ከነዋሪዎቹ ያገኘውን መረጃ መነሻ በማድረግ ስጋቱን ገልጿል ፡፡

ከዚህ ባሻገርም ብዙ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ላይ እንደሚገኙ ገልጾ ታሳሪዎቹ በሚገኙባቸው አንዳንድ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ በሚገኙ  እስር ቤቶች ውስጥ  አሳሳቢ የሆኑ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግሮች መስተዋላቸውን በመግለጫው ጠቁሟል፡፡ 

በሀገሪቱ የኮቪድ 19 መከሰት ተከትሎ የወጣው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ የህዘብን መሰረታዊ መብቶች እና ነጻነቶች፤ በተለይም የመሰብሰብ ነጻነትን  በከፋ ሁኔታ የሚገድብ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ የአዋጁ አተገባበር ወጥነት የጎደለው በመሆኑ የተነሳ በተለያዩ አካላት ቅሬታዎች እየቀረቡ መሆኑን ታዝበናል፡፡ በተለይም በመንግስት አካለት የሚጠሩ እና የሚዘጋጁ ስብሰባዎች ያለ ምንም እንቅፋት  ቁጥሩ ብዙ የሆነ ህዝብ እየተሳተፈ በመካሄድ ላይ ሲሆኑ በተቃራኒው ደግሞ ሌሎች አካለት በተለይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የተጠሩ የጋዜጣዊ መግለጫ እና ስብሰባዎች አጥጋቢ ያልሆኑ ምክንያቶች እየተሰጡ በጸጥታ ኃይሎች እንዲስተጓጎሉ መደረጉን እና በመንግስት በኩል የተወሰደው እርምጃም ተገቢ አለመሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገልፀዋል፡፡

በመሆኑም ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች  በኢትዮጵያ፤ መንግስት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የመፍትሔ  እርምጃዎች እንዲወስድ ጥሪ ያቀርባል፡-

  • የክልል እና የፌደራል የፀጥታ ኃይሎች የህግ የበላይነትን በማስከበር ረገድ ያላቸውን ሚና እና የዜጎችን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በቅጡ በመረዳት  በሰላማዊ መንገድ ሃሳባቸውን በሚገልጹ ወይም የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሚያደርጉ ዜጎች ላይ  የፀጥታ ኃይሎች ያልተመጣጠነ የኃይል እርምጃ እንዳይወስድ መንግስት ተገቢውን ክትትልና ጥንቃቄ እንዲያደርግ፤ እንዲሁም በጸጥታ ኃይሎች በተወሰዱ ያልተመጣጠነ የኃይል እርምጃዎች ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ተገቢውን ፍትህ እንዲያገኙ እና ያልተመጣጠነ ኃይል በሚጠቀሙ የፀጥታ አካላት ላይ ተገቢ እርምት መውሰድ ይኖርበታል፡፡የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን፣ የሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መንግስታት በተወሰዱ የኃይል እርምጃዎች እና በደረሱት ጉዳቶች ላይ በቂ እና አፋጣኝ ምርመራ በማካሄድ የምርመራቸውን ውጤት እና የተወሰዱ የእርምት እርምጃዎችን ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርጉ፣
  • የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያን ተከትሎ ጥቃቱ በተፈጸመባቸው አንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች  ለዳግም ጥቃት ስጋት ያለባቸው ነዋሪዎችን መንግስት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው፣ እንዲሁም የጥቃት ማስፈራሪያ እና ዛቻዎችን በሚያደርሱ ቡድኖች ላይ አስፈላጊውን ህጋዊ አርምጃ እንዲወስድ፣
  • በኦሮሚያ ከተከሰተው የሰላም መደፍረስ ችግር ስፋት አንፃር የእስር ሁኔታን በሚመለከት የመንግስት አቅም ውስንነት እንዳለ ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች  በኢትዮጵያ የሚገነዘብ ቢሆንም በቁጥጥር ስር የሚውሉ ሰዎች የአያያዝና ሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅ ሁኔታ ችላ ሊባል አይገባም፡፡ በመሆኑም መንግስት በተቻለ አቅምና ፍጥነት እነዚህን ችግሮች እንዲፈታ፣
  • የኮቪድ 19 መከሰት ተከትሎ የወጣው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አፈፃፀም  ያለ ምንም አድሏዊ አሰራር በመንግስት አካለትም ሆነ በሌሎች አካላት መካከል፤ በተለይም በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪክ ማህበራት ላይ በእኩልነት ተፈጻሚ እንዲሆን እና የዜጎችን መሰረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ሙሉ በሙሉ አደጋ ላይ በማይጥል መልኩ እንዲተገበር እናሳስባለን፡፡
Share this articleShare on Facebook
Facebook
Tweet about this on Twitter
Twitter
Share on LinkedIn
Linkedin
Share on Tumblr
Tumblr
Email this to someone
email

Filed Under: Home

Human Rights situation in Ethiopia in August 2020

10th September 2020 by Admin

Press Statement

September 10, 2020

Association for Human Rights in Ethiopia (AHRE) has issued this press statement on the basis of the major human rights situations in August 2020. AHRE is deeply concerned about the human rights situations in Ethiopia.

Government officials and several Human Rights defenders have confirmed that many civilians have been killed and injured in Wolita zone of the southern Nations, Nationalities and people’s region (SNNRP) in protests erupted following the request to establish separate statehood. As some reported, the use of excessive force by security forces has resulted in many deaths and injuries.

On the other hand, in the Oromia region, people lost their lives as a result of clashes between protestors and security forces. On a press statement released August 20, 2020 the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) called out for security forces to comply with their obligations and avoid using excessive force against protestors. 

Despite EHRC’s encouraging attempt to investigate the breach of peace and human rights violations that resulted from the murder of singer Hachallu Hundessa, a full report on the matter has yet to be given. A statement released on August 15, 2020 by the Commission noted that in some parts of Oromia, victims were still at risk of violence based on information received from the residents.

The statement further added that a large number of people have been apprehended and detained in prisons found in different parts of the Oromia region. The Commission also expressed deep concerns over human rights violation and treatment in some of these prisons. 

Following the outbreak of COVID-19 in the country the Ethiopian government has declared a state of emergency which is expected to limit basic human rights specially the right to public gatherings. However, Association for Human Rights in Ethiopia observed complaints from various parties about the inconsistency in the implementation of rules.  Several political parties called out the actions of the government to be unfair and partial concerning measures taken in off-putting press releases and meetings called by other bodies, especially political parties while meetings organized by the government faced no restrictions.

Therefore, Association for Human Rights in Ethiopia urges the authorities to:

  • Make sure that security forces comply with the standards of the rule of law and their responsibilities to serve and protect people and exercise the utmost restraint to avoid using excessive force on protestors who are acting within their rights.
  • We also urge authorities to carry out impartial investigations and prosecute those responsible for abuses and allow victims and their families to receive due justice.
  • We urge Ethiopian Human Rights’ Commission, Federal and Regional governments must conduct impartial and prompt investigation on allegations of abuses and notable excessive use of force and provide public reports on the results of their investigations and undertaken measures on those responsible.
  • Provide adequate protection to prevent further assaults on victims living in some parts of Oromia where the prior attacks took place following the assassination of Artist Hachallu Hundessa and take appropriate legal actions against groups that are carrying out threats and intimidations.
  • Given the gravity of the unrest, Association for Human Rights in Ethiopia understand the limitations on the capacity of the government on the context of the Oromia Crisis. However, the treatments and basic rights of detainees should not be neglected. Therefore, we ask the authorities to resolve these issues with urgency.
  • The implementation of the state of emergency following the outbreak of Covid-19 in the country should be carried out without any discrimination. We ask authorities to resolve impartial treatments against other bodies, specially opposition parties and civic societies and urge that fundamental rights and freedoms of citizens to be fully implemented.

Share this articleShare on Facebook
Facebook
Tweet about this on Twitter
Twitter
Share on LinkedIn
Linkedin
Share on Tumblr
Tumblr
Email this to someone
email

Filed Under: Home

በኦሮሚያ ክልል ብሔርን እና ሀይማኖትን መሰረት በማድረግ የተፈፀመው ጥቃት በገለልተኛ አካል ሊጣራ ይገባዋል!

3rd August 2020 by Admin

ጋዜጣዊ መግለጫ

ሐምሌ 26፣ 2012 ዓ.ም

የኢትዮጵያ መንግስት ገለልተኛ የሆኑ ባለሙያወችን እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንን ያካተተ ገለልተኛ አጣሪ ቡድን በማቋቋም ከአድሎ የፀዳ ምርመራ ሊያካሂድ ይገባል። 

የጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድን ወደ ስልጣን መምጣት ተከትሎ መንግስት በተለያዩ ዘርፎች ማሻሻያዎችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ከእነዚህም መካከል አፋኝ የሆኑ ህጎችን በማሻሻል የፖለቲካ እና የሲቪክ ምህዳሩን ማስፋት በዋነኝነት ይጠቀሳል፡፡ ይህም ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሃሳባቸውን በነፃነት በማራመድ ለሰብአዊ መብቶች መከበርና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ፤ እንዲሁም ለሀገር እድገት የበኩላቸውን አስተዋጽዎ እንዲያበረክቱ እድል ፈጥሯል፡፡ በሌላ በኩል መንግስት የሕግ የበላይነትን በማስፈን እና የዜጎችን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ ከፍተኛ የሆነ ቸልተኝነት አሳይቷል፡፡  በመሆኑም በሀገሪቱ በተለያዩ ጊዜያት በተከሰቱ ብሄርን እና ሀይማኖትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ሳቢያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ህይወታቸው አልፏል፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው የሕዝብ እና የአገር ሃብት እና ንብረት ወድሟል፤ እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከሚኖሩበት ቀያቸው ተፈናቅለው ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል፡፡    

በመንግስት ባለሥልጣናት ተደጋግሞ በመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው በያዝነው አመት ጥቅምት ወር የለውጥ አቀንቃኝ እና የሚድያ ባለቤት የሆኑት አቶ ጀዋር መሃመድ መንግስት ለጥበቃ የመደበለላቸውን የጥበቃ ሃይሎች ሊያነሳብኝ ነው፣ በታጠቁ ቡድኖች ተከብቤአለሁ በሚል ለደጋፊዎቻቸው ያስተላለፉትን የድረሱልኝ ጥሪ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል 97 ንጹሃን ዜጎች ሲገደሉ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ይሁንእና መንግስት የተፈጠረውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በአግባቡ በማጣራት ጥሰት ፈጻሚዎቹን ለፍርድ በማቅረብ እና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ፤ እንዲሁም በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች  አስፈላጊው ካሳ እንዲከፈላቸው እና ወደ ቀድሞ ሕይወታቸው እንዲመለሱ ማድረግ ሲገባው ነገሩን አለባብሶ ማለፉ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም መንግስት ህግ የማስከበር ግዴታውን በወቅቱ እና በአግባቡ ባለመወጣቱ፤ እንዲሁም  አስተማሪ የሆነ እርምጃ ባለመወሰዱ በዚሁ ክልልም ሆነ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ተመሳሳይ ባህሪ ያላቸው እና የከፋ የሰብአዊ መብት ቀውስና ጥሰት ያስከተሉ ክስተቶች በሰፊው እንዲፈፀሙ ምክንያት ሆኗል፡፡ 

በተጨማሪም ይህንኑ መንግስት ላይ እየታየ ያለውን ህግን የማስከበር እና አስፈላጊውን ቁጥጥር የማድረግ ክፍተት በመጠቀም አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ጥላቻን ሲሰብኩ እና ብሔርን እና ኃይማኖትን መሰረት ያደረገ ጥቃት በንፁሃን ዜጎች ላይ እንዲፈፀም ሲያነሳሱ ከርመዋል፡፡ በቅርቡም በሰኔ 22/2012 ዓ.ም. የኦሮምኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ እና የመብት ተሞጋች የሆነው አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ላይ የተፈጸመውን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች እና በአዲስ አበባ በተከታታይ ቀናት በተከሰተው ሁከት በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ዜጎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።  በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በየቤተ እምነቱ ለመጠለል ተገደዋል። በብዙ መቶ ሚሊዮኖች የሚገመት የሀገር ሀብት እና የግለሰቦች ቤት እና ንብረት በእሳት ወድሟል። በአዲስ አበባም አስራ አራት ሰዎች መገደላቸውና ከፍተኛ ግምት ያለው ንብረት መውደሙ ይታወቃል፡፡ 

የአይን እማኞች፣ የጥቃቱ ሰለባዎች እና ሌሎች የተለያዩ የመረጃ ምንጮች እንደሚያረጋግጡት ጥቃቱ ያነጣጠረው በክልሉ ውስጥ በሚኖሩ አነስተኛ ቁጥር ባላቸው የሌላ ብሄር ተወላጆች እና የክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ የነበረ መሆኑን ነው። ድርጊቱም የተፈፀመውም ጽንፍ በያዙ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆች እንደሆነ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ አብዛኞቹ ጥቃት ፈፃሚዎች ድርጊቱን ከጀርባ ሆነው በሚያቀናብሩ አካላት ተደግፈው እና  የመጓጓዣ አገልግሎትም  ተመቻችቶላቸው እንደነበር እና ጥቃቶቹ ከተፈፀሙባቸው አካባቢዎች ውጪ ካሉ ሥፍራዎች የመጡ ወጣቶች መሆኑን እማኞች መስክረዋል። ጥቃቱን ያደረሱትም ግለሰቦች በደንብ የተደራጁ፣ ቀድሞ በተጠና እና ዝግጅት በተደረገበት  መልኩ ይንቀሳቀሱ እንደነበር ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች ያረጋግጣሉ።  በአንዳንድ ሥፍራዎች እነዚሁ ቡድኖች ኢላማ ያደረጉዋቸውን ሰዎች የስም ዝርዝር ቀድመው በመያዝ እና ከቤት ቤት እየተንቀሳቀሱ ጥቃት ይፈጽሙ እንደነበርም  መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ እነዚህ አጥፊዎች የሌላ ብሄር ተወላጅ የሆኑ ነዋሪዎችን ብቻ ሳይሆን የክርስትና እምነት ተከታይ የሆኑ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችንም ጭምር የጥቃት ኢላማ በማድረግ ግድያና ንብረት ማውደም መፈጸማቸውን ማረጋገጥ ተችሏል። በተወሰኑ አካባቢዎች የእስልምና ተከታይ የሆኑ የአካባቢው ተወላጅ ያልሆኑ ዜጎች ንብረትም ወድሟል። ሙሉ ለሙሉ ከወደሙት እና ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ንብረቶች እና መሰረተ ልማቶች መካከልም ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ ትላልቅ የንግድ ተቋማት፣ ፋብሪካዎች፣ ሆቴሎች እና በርከት ያሉ የመኖሪያ ቤቶች ይገኙበታል፡፡  

በተጨማሪም በአንዳንድ አካባቢዎች ጥቃት አድራሾቹ  የጥቃት ሰለባ ያደረጎቸውን ግለሰቦች አካል በመቆራረጥ እና እጅግ አሰቃቂ በሆነ መልኩ አሰቃይተው በመግደል፤ እንዲሁም የሟቾቹን አስክሬን መንገድ ለመንገድ በመጎተት ከሰው ልጅ ስብእና በወጣ መልኩ በድል አድራጊነት ስሜት ሲጨፍሩ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ቤት ንብረታቸው የተቃጠለባቸው እና መግቢያ ያጡ፤ እንዲሁም ስጋት ያደረባቸው በሺዎች የሚገመቱ ዜጎች በተለያዩ የእምነት ተቋማት ውስጥ እና ሌሎች ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሚያጋልጥ መልኩ ተፋፍገው እንደሚገኙም ይታወቃል፡፡  

ይህ ሁሉ እልቂት እና የሃብት ውድመት ሲደርስ መንግስት አስፈላጊውን የመከላከል እና ጥቃቱን በአፋጣኝ የማስቆም እርምጃ መውሰድ ባለመቻሉ የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት በመጠበቅ እረገድ በአገሪቱ ሕገ መንግስት እና በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች የተጣሉበትን ግዴታዎች ሳይወጣ ቀርቷል፡፡ የመንግስት የመገናኛ አውታሮችን ጨምሮ በተለያዩ ምንጮች እንደተገለፀው ግጭቶቹ በተከሰቱበት በአብዛኞቹ አካባቢዎች የሚገኙ የጸጥታ አስከባሪ ኃይሎች እና የአካባቢዎቹ መንግስታዊ መዋቅሮች ዝምታን መርጠዋል። በተለይም የፀጥታ አካላት የተቋቋሙበትን አላማ በመዘንጋት እና ከበላይ ትዕዛዝ አልተሰጠንም በሚል ተቀባይነት የሌለው ሰንካላ ምክንያት አደጋውን የማስቆም እና ጥቃቱን የመከላከል እርምጃ በአፋጣኝ ሳይወስዱ ቀርተዋል፡፡ ብሎም በአንዳንድ ችግሩ በተከሰተባቸው አካባቢዎች የፀጥታ አካላት መሳሪያቸውን ለጥቃት ፈፃሚዎቹ እስከመስጠት ድረስ የደረሰ እገዛ እና ድጋፍ ሲያደርጉ እንደነበር በክልሉ ባለስልጣናት ተገልጧል፡፡ ይህም አገር አማን ነው ብለው እና ለደህንነታቸው ጥበቃ የሚያደርግላቸው መንግስት መኖሩን አምነው በክልሉ የሚኖሩ የሌላ ብሔር ተወላጆች እና የክርስትና እምነት ተከታዮች በክልሉ የመንግስት መዋቅር ላይ አመኔታ እንዲያጡ እና የደህንነት ስጋትም እንዲሰማቸው አድርጓል፡፡ 

በአሁኑ ወቅትም መንግስት የአካባቢውን ሰላም እና ፀጥታ እንደሚያስከብር፤ እንዲሁም ለተጎጂዎች ፍትህን እንደሚያረጋገጥ ቃል በመግባት እንቅስቃሴዎችን እያደረገ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ተጠርጣሪዎችንም፤ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጧል፡፡ ይሁንና ከላይ እንደተገለፀው አንዳንድ በክልሉ መንግስት በተለያየ ደረጃ ያሉ አመራሮች የጥቃቱ ደጋፊ እና እንዲሁም በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ በመሆናቸው ጉዳዩ ከወገንተኝነት በፀዳ እና ገለልተኛ በሆነ አካል ሊጣራ እና መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል፡፡ በተጨማሪም በሀገሪቱ ፅንፍ የወጣ ብሄርተኝነት እና የሀይማኖት አክራሪነት ስር እየሰደደ እንደመምጣቱ እና ጥቃቱ ብሔር እና ኃይማኖት ተኮር እንደመሆኑ ትክክለኛ ፍትህን ለማስፈን እና ለችግሩ በማያዳግም ሁኔታ መፍትሄ ለማበጀት ይረዳ ዘንድ የደረሰውን ጉዳት የሚያጣራ እና ለሀገር አንድነት የሚጠቅም መፍትሄ የሚያስቀምጥ ገለልተኛ አካል ተዋቅሮ ጉዳዩን እንዲመረምር፣ መረጃዎችን እንዲያሰባስብ እና በምርምር ላይ የተመሰረተ የውሳኔ ሃሳብም እንዲያቀር ማድረግ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ 

በመሆኑም ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች  በኢትዮጵያ፤ መንግስት እና የአለም አቀፍ ማህበረሰቡ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የመፍትሔ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጥሪ ያቀርባል፡፡ 

ለኢትዮጵያ መንግስት 

  • ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በተለያዩ የእምነት ተቋማት እና መጠለያዎች ተጠልለው ለኮቪድ-19 በሚያጋልጥ ሁኔታ ለሚገኙ ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ እና እርዳታ እንዲያደርግ፤ መልሰው የሚቋቋሙበትንም ሁኔታ እንዲያመቻች፣
  • ገለልተኛ የሆኑ ባለሙያወችን እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንን ያካተተ ገለልተኛ ቡድን በማቋቋም ከአድሎ የፀዳ ምርመራ እንዲያካሂድ፣ 
  • እየተካሄዱ የሚገኙ ምርመራዎች እና የማጣራ ሥራዎች በህግ አግባብ እየተከናወኑ መሆኑን እንዲያረጋግጥ እና በህግ ጥላ ስር የዋሉትንም ተጠርጣሪዎች በህጉ መሰረት ለፍርድ እንዲያቀርብ፣  
  • በህግ አግባብ ምዝገባ ሳያከናውኑ የሚንቀሳቀሱ እና አላማቸውም ጥላቻን መስበክ፣ ፅንፈኝነትን እና ግጭቶችን ማባበስ የሆኑ የሲቪል ማህበራት እና የፖለቲካ ድርጅቶች ነቅሶ በማውጣት፤ እንዲሁም የገንዘብ ምንጮቻቸውን በመለየት ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ፣
  • በህዝቦች መካከል መቃቃርን የሚፈጥሩ እና ለግጭት የሚጋብዙ የጥላቻ ንግግሮችን እና መልዕክቶችን  የሚያስተላልፉ  መገናኛ ብዙሃንእና ማህበራዊ ድህረ ገፆች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ፣ 
  • በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወደ ሀገር ገብተው ሳለ አሁንም ታጥቀው የሚገኙ እና በተለያዩ ጊዜያት ጥቃቶችን እየፈፀሙ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የተደራጁ ቡድኖች ትጥቅ እንዲያስፈታ፣ 
  • የክልል እና የፌደራል የፀጥታ ኃይሎች ህግን በማስከበር ረገድ ያለቸውን ሚና እና የተጣለባቸውን ኃላፊነት  የሚያትት መመሪያ እንዲያወጣ፣
  • ለተጎጂዎች እውነተኛ ፍትህን እንዲያሰፍን፣ አስፈላጊውን ካሳ እንዲከፍል እና በየትኛውም አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ደህንነት በማያወላዳ ሁኔታ እንዲያስከብር፣
  • የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን እንዲከላከል፣ ጥሰቶች ተፈፅመው ሲገኝ ደግሞ በአግባቡ እና በወቅቱ እንዲያጣራ እንዲሁም በፈፃሚዎች ላይ በህግ አግባብ አስተማሪ የሆኑ እርምቶችን እንዲወስድ እናሳስባለን። 

ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች 

  • የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረውን ብሔርን እና ኃይማኖትን መሰረት ያደረገ እና በመቶዎች ለሚቆጠሩ ንፁሃን ዜጎች ህልፈት፣ በብዙ መቶ ሚሊዮኖች ለሚገመት ንብረት ውድመት እና ከአስር ሺዎች በላይ ለሚሆኑ ዜጎች መፈናቀል ምክንያት የሆነውን ጥቃት በገለልተኛ አካል እንዲጣራ እንዲያደርግ እና በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩ ዜጎችን ደህንነት እንዲስጠብቅ ግፊት እንዲያደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ 
Share this articleShare on Facebook
Facebook
Tweet about this on Twitter
Twitter
Share on LinkedIn
Linkedin
Share on Tumblr
Tumblr
Email this to someone
email

Filed Under: Home

  • « Previous Page
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • …
  • 28
  • Next Page »

Subscribe

Sign up to receive email updates

Previous Posts

AHRE’s statement for the 72th Human Rights Day

በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለው ሰብአዊ ቀውስ እና በዜጎች ማንነት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች አስቸኳይ መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል!!!

The humanitarian crisis of the war and ethnic-based attacks on the identity of citizens must be addressed!!!

Association for Human Rights in Ethiopia September 2020 Press release

የመስከረም ወር 2013 ዓ/ም ጋዜጣዊ መግለጫ

የነሐሴ ወር 2012 የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በኢትዮጵያ