Association for Human Rights in Ethiopia

  • About
  • Key Resources
  • Publications
  • Archives
  • Contact Us
  • Ethiopia: Killings, arrests under new State of Emergency
  • Ethiopia arrests 30 journalist, bloggers and activists
  • Joint civil society letter to Ethiopian Prime Minister-designate on recent arrests of journalists and human rights defenders
  • Joint civil society letter to Ethiopian Prime Minister-designate on recent arrests of journalists and human rights defenders
  • Facebook

Powered by Genesis

መንግስት ለዜጎች ደህንነት ጥበቃ የማድረግ ሃላፊነቱን ይወጣ! አሳሳቢው እና ተደጋጋሚው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና የዜጎች እልቂት

15th April 2021 by Admin

ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ በሃገራችን በተደጋጋሚ በዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት በማድረግ እየተፈፀሙ ያሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች አስከፊ ደረጃ እየደረሰ መሆኑን ድርጅታችን በተደጋጋሚ ባወጣቸው ጋዜጣዊ መግለጫዎች ላይ ገልጿል። አያይዞም ስጋቱን  በመንግስትና ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት በኩል ምን እርምጃ መወሰድ እንዳለበት በተደጋጋሚ ሲያሳስብ እንዲሁም ምክረ ሃሳቦችን ሲሰጥም ቆይቷል።

ዜጎች መብታቸው እና ነፃነታቸው ተረጋግጦ የመኖር ህጋዊ እና ተፈጥሮአዊ መብት እንዳላቸው እሙን ነው፡፡ ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በዜጎች ላይ የሚሰነዘሩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲሁም እጅግ አስከፊ እና ተደጋጋሚ የሆኑ  ጭፍጨፋ እና እልቂቶች ስር እየሰደዱ  ይገኛሉ፡፡

ከየካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም  ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ጃርቴ  ወረዳ ደቢስ ቀበሌ በርካታ ንጹሃን ዜጎች በግፍ እና በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ፣ አካል ማጉደል ፣ የንብረት ዘረፋ እና መፈናቀል  እንደተፈፀመባቸው እንደ ቪኦኤ ባሉ እና ሌሎች ሚድያዎች መሰረት መረጃዎች ወጥተዋል፡፡ በተመሳሳይ በዚሁ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ገንቤል ወረዳ በሶስት የዞኑ አካባቢዎች ላይ በመጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም መጠነ ሰፊ የሆነ እና ማንነትን መሰረት ያደረገ ጭፍጨፋ በአማራ ተወላጆች ላይ መድረሱ በተለያዩ ሚዲያዎች ማለትም በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ፣ አዲስ ስታንዳርድ እና በሌሎችም ተዘግቧል፡፡

በሌላ በኩል ተደጋጋሚ የዜጎች እልቂት እየተስተናገደበት ባለው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል እና ካማሼ ዞን ከመጋቢት 22 እና 23 ቀን 2013 ዓም ጀምሮ በንጹሃን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት ያደረጉ የጥቃት እርምጃዎች ተፈጽመዋል። ድርጊቶቹም የበርካቶች ሕይወት የቀጠፉ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ጥቃቱን ፈርተው የተሰደዱ እና በጥቃቱ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውም ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ ነው።ባለፉት ጥቂት ቀናትም ይህ ድርጊት መቀጠሉን  እና ዜጎችም ለተደጋጋሚ ጥቃት መጋለጣቸውን በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ጭምር ቀርበው ስጋታቸውን እና አቤቱታቸውን እያሰሙ ይገኛሉ። ይህን መሰል በማንነት ላይ ያተኮሩ ጥቃቶች መደጋገም እና ዛሬም ንጹሃን ዜጎች ስጋት ውስጥ ሆነው መንግስት እና ሌሎች አካላት እንዲታደጓቸው ጥሪ እያቀረቡ መሆኑ ድርጅታችንንም በጥልቅ አሳስቦታል፡፡

ይህ ማንነትን መሰረት ያደረገ እልቂት በተመሳሳይ በአማራ ክልል አጣዬ፣ ሸዋ ሮቢት፣ ኬሚሴ፣ ማጀቴ እና አካባቢው ላይ ባሉ ወረዳዎች ተከስቶ በንጹሃን ዜጎች ላይ መጠነ ሰፊ ጉዳት አድርሷል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በመጋቢት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው ሪፖርት በእነዚህ አካባቢዎች  በደረሰ ጥቃት 104 ሰዎች መገደላቸውን እና ሶስት ቤተክርስቲያኖች፤ አንድ ትምህርት ቤት መቃጠላቸውን እንዲሁም ከመቶ በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸውን አመላክቷል፡፡ በተጨማሪም በአንቡላንስ ለህክምና በመወሰድ ላይ የነበሩ ቁስለኞች ከአንቡላስ እንዲወርዱ ተደርገው ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተገድለዋል፡፡

በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ከመጋቢት 24 ቀን 2013 ዓም ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭት እስከ 100 የሚደርሱ ሰዎች ህይወት ማለፉን እና የንብረት ውድመት መድረሱን እንደ ዶይቸ ቬለን ያሉ የተለያዩ ሚድያዎች የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ከፍተኛ የዜጎች ህይወት መጥፋት እንደምክንያት የተነሳው የድንበር ጉዳይ መሆኑ ተዘግቧል፡፡

በሀገሪቱ የሚከሰቱ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች አድማሳቸውን እያሰፉ እና እየተባባሱ መምጣታቸውን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች ከቀያቸው እየተፈናቀሉ ይገኛሉ፡፡

ላለፉት ሁለት አመታት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ተከታታይ በሆነ መልኩ በዜጎች ህይወት ላይ ያነጣጠሩ የጅምላ ጭፍጨፋዎች መከሰቱ የአገሪቱን የሰብአዊ መብት አያያዝ ወደ ከፋ ደረጃ አድርሶታል። ዜጎች ለህይወታቸውም ሆነ ላፈሩት ንብረት ደህንነት ዋስትና ሊሰጣቸው የሚችለው መንግስት እንደሆነ ይታወቃል። ይሁንና በተለያየ ደረጃ ላይ ያሉ የመንግስት አካላት እነዚህን አደጋዎች ቀድሞ ለመከላከልም ሆነ ድርጊቶቹ ከፍተኛ ጉዳት ሳያስከትሉ በፊት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ተመጣጣኝ እና ሕጋዊ እርምጃዎችን ባፋጣኝ ሲወስዱ አይሰተዋሉም። ይህ አይነቱ በመንግሥት አካላት በኩል የሚስተዋለው ከልክ ያለፈ ቸልተኝነት ወይም ኃላፊነትን በአግባቡ ያለመወጣት ችግር የአገሪቱን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ወደከፋ ደረጃ ላይ ያደረሰው መሆኑን በርካታ ጥናቶች እና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች መግለጫዎች ያመላክታሉ።

በአገራችን እየከፋ የመጣው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በንጹሐን ዜጎች ላይ ያነጣጠሩና በየዕለቱ የሚፈጸሙ እጅግ ሰቅጣጭ የጅምላ ግድያዎች እና መፈናቀሎች ከሌሎች የፖለቲካ ቅራኔዎች ጋር ተደማምረው አገሪቱን ወዳልተረጋጋ የግጭት ቀጠና እየቀየሯት ይመስላል።  በተለይም በኦሮሚያ ክልል ወለጋ፤ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል እና ካማሸ ዞን እንዲሁም በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን እና በሰሜን ሸዋ አዋሳኝ አካባቢዎች ክቡር የሆኑ የሰው ልጆች በየቀኑ የሚገደሉበት እና ለተዳጋጋሚ ጥቃት የሚጋለጡበት በሰዎች ላይ አስከፊ እና ዘግናኝ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የሚፈፀሙባቸው፣ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችቤትና ቀያቸውን ለቀው ለመፈናቀል የሚገደዱበት አካባቢዎች መሆን ከጀመሩ ሰነባብተዋል::

 ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ ባለፉት ተከታታይ ወራት ባወጣቸው ተመሳሳይ መግለጫዎቹ መንግስት እነዚህን መሰል ጥቃቶችን እና ግጭቶችን እንዲያስቆም እና ምን የመፍትሔ እርምጃዎችን ቢከተል የተሻለ እንደሚሆን ጭምር ስንጠቁም እና ደጋግመንም ስንወተውት ቆይተናል። ይሁንና ችግሮቹ ተገቢውን ያህል ትኩረት ሊያገኙ ባለመቻላቸው አድማሳቸውን እያሰፉ እና የተጎጂውን ማህበረሰብ ቁጥር እየጨመረ፤ እንዲሁም የጥቃቱ አይነት እና የጭካኔውም ደረጃ እየከፋ መምጣቱን በቅርብ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተከሰቱ የመብት ጥሰቶች ከበቂ በላይ አስረጂዎች ናቸው።

እንደ ድርጅታችን እምነት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲቀንሱ፣ እንዲቆሙ እና እንዲሻሻሉ ከሚረዱት ስልቶች አንዱ በመብት ጥሰት ፈጻሚነት የተሳተፉ አጥፊዎችን እና ተባባሪዎቻቸውን በሕግ አግባብ ተጠያቂ ማድረግ ሲቻል ነው። በመንግስት የተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ላይ የሚገኙ አካላት ላይ በቂ ምርመራ ተወስዶ አጥፊዎች ተጠያቂ የሚሆኑበት ግልጽ እና ፍትሃዊ አሠራር አለመዳበሩ ጥፋት አጥፍቶ ያለመጠየቅ ባህልን ከማጎልበትም አልፎ ዜጎች በፍትህ እጦት እንዲሰቃዩም ምክንያት ይሆናል። ተጠያቂነትን ባለማስፈን ምክንያት እየተበራከተ የሄደው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ድርጅታችንን በእጅጉ ያሳስበዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተቋማችን መንግስት ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሰብአዊ መብቶችን የማክበር፣ የማስከበር እና የማዳበር ግዴታዎቹን በአግባቡ መወጣት የሚያስችለውን ስልት እንዲቀይስ እና ተጠያቂነት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ማስገንዘብ ይወዳል፡፡

ስለሆነም ተቋማችን መንግስት የሚከተሉትን የመፍትሄ እርምጃዎች እንዲወስድ ጥሪውን ያቀርባል፡-

  • ከመቼውም ጊዜ በላይ በቂ ትኩረት በመስጠት እየተከሰቱ ያሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በአፋጣኝ እንዲያስቆም፣ የቅድመ መከላከል ስራዎችን እንዲሰራ እና የዜጎችንም ህይወት መታደግን ቅድሚያ እንዲሰጥ፤
  • በተደጋጋሚ አስከፊ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተከሰተባቸው ባሉት አካባቢዎች አስፈላጊውን ህዝባዊ እና ተቋማዊ መፍትሄዎችን እንዲወስድ፤
  • ዜጎች በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢዎች በሰላም የመኖር፣ የመስራት እና ንብረት የማፍራት መብታቸውን እንዲያረጋግጥ እና ለዜጎች ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግ፤
  • በሰዎች ላይ አስከፊ የሰብአዊ ጥሰት እየፈፀሙ ባሉ ግልሰቦችና ቡድኖች እንዲሁም በተባባሪዎቻቸው ላይ ሕጋዊ  እና  ለድርጊቶቹ ተምጣጣኝየሆነ  እርምጃ እንዲወስድ
  • አስከፊ የሆነው ሀገራዊ የሰብአዊ መብት ጥሰት ጉዟችን ይቆም ዘንድ ሃገራዊ የውይይት እና የምክክር መድረኮችን እንዲፈጥር፤

ከቀያቸው ተፈናቅለው ለሚገኙ ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ እና ከትትል እንዲያደርግእናሳስባለን

ድርጅታችን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ እንዲሻሻል ችግሮችን በአግባቡ አጥንቶ ለመንግስት ጥቆማና ምክረ ሃሳቦችን ከመስጠት ጀምሮ  ዜጎች መብቶቻቸው እና ግዴታዎቻቸውን አውቀው የራሳቸውን መብት እንዲያስከብሩ እና የሌሎችንም ሰዎች መብት እንዲያከብሩ በማስተማር የበኩሉን ጥረት ያደርጋል።

Share this articleShare on Facebook
Facebook
Tweet about this on Twitter
Twitter
Share on LinkedIn
Linkedin
Share on Tumblr
Tumblr
Email this to someone
email

Filed Under: Home

በትግራይ ክልል ከጦርነት ማግስት በዜጎች ላይ እየተፈፀሙ ያሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መንግስታዊ ትኩረትን ይሻሉ!!

22nd March 2021 by Admin

ጋዜጣዊ መግለጫ

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በትግራይ ክልል የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና ሰፊ የሆነ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት አለመሟላት በዜጎች ላይ እያስከተለ ያለው ጉዳት ድርጅታችንን እጅጉን ያሳስበዋል፡፡ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትን በተመለከተ  ምንም እንኳን በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራበት ያለ ጉዳይ ቢሆንም በጦርነቱ ከደረሰው ሰፊ ጉዳት ጋር ሲነጻጸር ተመጣጣኝ አለመሆኑን የተለያዩ ሪፖርቶች እየወጡ ነው። በጦርነቱ እና ጦርነቱን ተከትሎ ለተወሰነ ጊዜ በተከሰተው የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት መስተጓጎል  የተነሳ በርካታ ዜጎች ለአስከፊ የሰብአዊ መብት ቀውስ መዳረጋቸውን የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ የበርካታ አለም አቀፍ ተቋማት ዘገባዎች ያረጋግጣሉ፡፡ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ ድጋፍ ሰጪ አካላት እና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ባወጧቸውም ዘገባዎች እና ሰፊ የዳሰሳ መግለጫዎች መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ እርምጃዎች እንዲወስድ በመወትወት ላይ ይገኛሉ።

በሌላ ኩነት ደግሞ በማናቸውም አካላት የሚፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ግድያዎች እና ህጋዊ ያልሆኑ እርምጃዎች ትኩረት ሊሰጣቸው፣ እርምት ሊደረግባቸው እንዲሁም ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ ሊደረግላቸው እና አጥፊዎች ለህግ እንድቀርቡ ማድረግ ይገባል፡፡

በተጨማሪም በትግራይ ክልል የሚገኙ ንጹሃን ዜጎች የመንቅሳቅስ እና የደህንነት ጉዳይ ልዩ ትኩረትን ያሻል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቅቀው በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ታጅበው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ የነበሩ ተማሪዎች  የካቲት 11/2013 በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ ስድስት ተማሪዎች ሕይወታቸው ማለፉን እና ብዙዎች መቁሰላቸውን ተዘግቧል፡፡ 

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል የተከሰተውን  የሰብአዊ ቀውስ ለማስተካከል በሚደረገው እርብርብ የሚሳተፉ ድርጅቶች ትኩረት በሚፈልጉ ቦታዎች ላይ ለመድረስ የተለያዩ ጥያቄዎችን እና ፈቃዶችን እየጠየቁ ይገኛሉ፡፡ ምንም እንኳን መንግስት ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ በቅርቡ አዎንታዊ ምላሽ የሰጠ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ የሰብአዊ ቀውሱን ለመቆጣጠር እና ዜጎች ጊዜውን የጠበቀ እገዛ ያገኙ ዘንድ መንግስት ጥያቄዎችን በአዎንታዊ እና ፈጣን በሆነ መልኩ ምላሽ እንዲሰጥ እንመክራለን፡፡

በተጨማሪም በዚሁ ክልል በሴቶች ላይ አስከፊ የሆነ ፆታዊ ጥቃት እየደረሰ መሆኑን የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የካቲት 04/2013 ዓ.ም ባወጣው ዘገባ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎቸ ጦርንቱ በተጀመረ ሁለት ወራት ብቻ 108 ፆታዊ ጥቃቶች መመዝገባቸውን ያወጣ ሲሆን እነዚህ ድርጊቶች የበርካታ ንፁሃን ሴቶችን ህይወት የሚያጨልሙ እና መሰረታዊ የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰትን የሚያስከትሉ በመሆናቸው ድርጅታችንን ያሳስበዋል፡፡

በመሆኑም ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች  በኢትዮጵያ፤ መንግስት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የመፍትሔ  እርምጃዎች እንዲወስድጥሪ ያቀርባል፡-

  • በትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻውን ተከትሎ ዜጎች ለሰብአዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን ወይም አለመፈፀሙን በገለልተኛ አካል ተጣርቶ በጉዳዩ ተሳትፎ የነበራቸው አካላት ለህግ የሚቀርቡበትንንና ተጎጂ ዜጎች ተገቢውን ካሳ የሚያገኙበትን ሁኔታ መንግስት እንዲያመቻች፤
  • በክልሉ የተከሰተውን የሰብአዊ ቀውስ እልባት እንዲሰጥ እና በዚሁም እገዛ ማድረግ ለሚፈልጉ አካላት ምቹ ሁኔታን እንዲፈጥር፤
  • በክልሉ የሚኖሩ ዜጎችን እና በህይወት የመኖር፣ የንብረት ጥበቃ እና በሰላም የመንቀሳቅስ ዋስትና እንዲሰጥ፤
  • በክልሉ ውስጥ ለሚንቅሳቀሱ እና ለጥቃት ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉ ዜጎች የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ አስትማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ
  • በሴቶች ላይ የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃቶችን በአስቸኳይ እንድያስቆም እንድሁም የጥቃት ሰለባ የሆኑ ሴቶች ተገቢውን እርዳታ እና እገዛ እንዲያገኙ እንዲሁም የጥቃቱ ፈጻሚዎች ለህግ እንዲያቀርቡ እንድያደርግ ስበስብ ለሰብአዊ መብቶች ያሳስባል፡፡
Share this articleShare on Facebook
Facebook
Tweet about this on Twitter
Twitter
Share on LinkedIn
Linkedin
Share on Tumblr
Tumblr
Email this to someone
email

Filed Under: Home

Grave Human rights violations against civilians in Tigray Region need government’s attention!!

22nd March 2021 by Admin

Press Statement

Association for Human rights in Ethiopia has been seriously following the major events concerning the human rights issues in the country and release multiple press statements on the necessary measures to be taken. Similarly, AHRE is releasing this press statement on basic human rights issues occurring in Tigray Region.

The Humanitarian crisis resulted from the war in Tigray Region

AHRE is deeply concerned about the grave human rights violations and lack of access to humanitarian assistance that is caused following the war in the Northern part of the country, Tigray Region. Although there are efforts from the government to provide humanitarian access to the affected areas, various reports have shown that it is far from being sufficient to cover the extensive damage inflicted by the war. As confirmed by reports from numerous international organizations including the United Nations, the war and events following the war stalled humanitarian assistance in the area exposing civilians to severe human rights abuses. Humanitarian organizations, aid groups and Human Rights Organization released reports and detailed reviews are urging the government to take immediate actions on the matters.

On the other hand, the government should pay attention human rights violations, killings and illegal acts by any party, protect its citizens and bring perpetrators to justice.

In addition, special attention must be given to the movement and safety of innocent citizens in the Tigray region. In this regard, it was reported that students from Adigrat University who have completed their studies and were being escorted back to their families by government security forces were attacked in a shooting by gun men on February 11,2013 leaving six students dead and others injured.

On the other hand, organizations engaged in the effort to address the humanitarian crisis in Tigray region are raising questions and requesting permits to be able to reach places in need of immediate attention. Although the government has recently responded positively in this regard, we advise the government to give positive and timely response to the organizations’ requests to help control the humanitarian crisis and allow citizens receive the necessary aid on time.

In addition, there are also reports of sexual violence against women in the region. A report by the  Ethiopia Human Rights Commission (EHRC) released on February 11, 2021 shown 108 cases of sexual assaults in just two month since the war erupted. Our organization is concerned that these assaults are violations against fundamental human rights and have the potential to destroy the lives of many innocent women. 

Therefore, Association for Human Rights in Ethiopia calls on the government to take the following remedial measures:

  • To facilitate the opportunity for independent parties to investigate the claims of human rights violations in the Tigray region following the law enforcement operation in Tigray region and hold the responsible parties accountable and to ensure the victims receive the appropriate compensation.
  • To address the humanitarian crisis in the region and create a conducive environment for parties interested in assisting the area.
  • To guarantee the safety of the lives, properties and movement of the people in the region,
  • To guarantee the safety and provide reliable protection for vulnerable population and movement of citizens in the region.
  • To put an immediate stop on the sexual violence against women and provide the necessary assistance to victims and hold the responsible parties accountable.
Share this articleShare on Facebook
Facebook
Tweet about this on Twitter
Twitter
Share on LinkedIn
Linkedin
Share on Tumblr
Tumblr
Email this to someone
email

Filed Under: Home

  • 1
  • 2
  • 3
  • …
  • 29
  • Next Page »

Subscribe

Sign up to receive email updates

Previous Posts

የዜጎች ማንነትን መሰረት አድርገው ጥቃት እየፈፀሙ የሚገኙ ግለሰቦችንና ቡድኖችን መንግስት በህግ ተጠያቂ ሊያደርግ ይገባል፡፡

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ማንነት መሰረት አድርገው የሚደርሱ ተደጋጋሚ ጥቃቶቸን መንግስት ሊያስቆም ይገባል!!!

The government must stop the repeated identity-based attacks occurring in Benishangul-Gumuz Zone!

AHRE’s statement for the 72th Human Rights Day

በጦርነቱ ምክንያት እየደረሰ ያለው ሰብአዊ ቀውስ እና በዜጎች ማንነት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች አስቸኳይ መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል!!!

The humanitarian crisis of the war and ethnic-based attacks on the identity of citizens must be addressed!!!